Posts

Showing posts from June, 2014

ያኔ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያው ሰሞን

መቼም እንደያኔው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የጦቢያ ባንዲራና የዋልያዎቹ መለዮ በቲሸርት፣በቁምጣ፣በቦዲ.. በፕላስቲክ አንባር ጠንከር ሲልም ግልጥ በሚታዩ ልባሶች፣ ጡት ማስያዥያ የሚመስሉ ነገሮች ሳይቀሩ ማለት ነው፡፡ ያኔ የተለመደውን ዙሪቴን ለማድረግ በአራት ኪሎ በኩል ወዳጆቼን ለማግኘት ዘልቄ ነበር፡፡ ነገር ግን የወዳጄቼን መቆየት አስታክኬ አንድ ጥግ ላይ ቁጭ ብለው ‹‹እ!..አለ የሚቀባ..ቀለም፣ቀለም…›› የሚሉ ወጣቶች ልጆች ወሬያቸው ሳበኝና ጠጋ ከማለቴ፣ ‹‹ነይ ቀዮ ይህን ቀይ ፌስሽን ላሸብርቀው በናት ሀገራችን ቀለም!›› ሳቅ እንደያዘኝ ‹‹ አታሸብርቀው ..ግን ሰው እየጠበቅኩነው፤ሰትቀቡም ለማየት ነው›› አልኩት ‹‹አብሽር ዱቅ በይ›› አለኝ፡፡ ቀለሙ ከምን እንደሚሠራ፣ማን እንዳመጣው ባይገባቸውም ብቻ ለዛሬም ቢሆን ለነዚህ ወጣቶች ትልቅ ገቢ ነው፡፡ ከሌላ አቅጣጫ ፊቱን በቀለም አዥጎርጉሮ የሚመጣውን ጓደኛቸውን ሲያዩት ፣ተንጫጩ፣የተረብ ናዳውን አወረዱት፤ ‹‹አንተ አንገትህን ዝቅ አግርገው ነው እንዴ የነከሩህ›› አለው አንዱ ሌላኛው ‹‹ ኒያላ ነው የምትመስለው እንኳን ዋልያ ልትመስል››   አንዱ ተቀበለና ‹‹አንተ እኮ ባትቀባም ዋልያ ትመስላለህ›› ፤ሳቅ በሳቅ ሆንን፡፡ ትንሽ ቆይቶ ደግሞ…                                            ‹ ‹ለከፋና   ሽቀላ››   እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም ለከፋና ሽቀላ አብረው የሚሄዱ የዘመኑ ትዕይንቶች ናቸው፡፡ ቀለም ከሚቀቡት ወጣቶች አንደኛው አፉ የማያርፍ ዓይነት ነው፡፡ አላፊ አግዳመውን ለቀለም ከመጋበዝ ባለፈ ተረብም ጣል ያደርጋል፡፡ አንዲት ኮረዳ ቢጤ ብቅ ስትል፤ ‹‹እናቱ ልቀባልሽ…ውይ ይቅርታ ልቀባሽ›› ተሳሳቁ፡፡ በግልምጫ አንስታው አለፈ

አያቴ

በልጅ አዕምሮዬ ውስጥ ትልቅ የትዝታ ስዕል ስለውብኝ ካለፉት ሰዎች መካከል አልፎ አልፎ ወደ ኋላ መለስ ብዬ ከማጣጥማቸው መልካም ትዝታዎቼ ውስጥ የእናቴ አባት አንዱ ነው፡፡ ከተረቶቹና ምሳሌዎቹ፣ከማያልቁት ወጎቹ፣ከምንም በላይ ደግሞ ተረብ አዋቂነቱ ብዙ የሕይወት ፍልስፍናዎችን አስዘርፎኛል፡፡ ከምንም በላይ የምቀናበት በሰባዎቹ መጨረሻ ሆኖ የነበረው ጤነኝነትና ጥንካሬ፣ የሥራ ፍቅር ከወዲያኛው ዘመን ጠንካራና ጤናማ ሕይወትን በደግ ዘመን ካጣጣሙት የአቢሲኒያ ልጆች ሕይወትን ቁልጭ አድርጎ ያሳየኝ ሕያው መስታወት ነበር ማለት እችላለሁ፡፡ ስንቶቻችሁ ሰለ አያቶቻቹ ጥልቅ የሆነ ጥዑም ትዝታ እንዳላችሁ ባላውቅም እኔ ግን ከተማርኳቸው ብዙ ቁም ነገሮች ጥቂቶቹን እንካችሁ ልላችሁ እችላለሁ፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ በግጥም የሚለግሰኝ ጥልቅ ምክሮች ዛሬ ላይ ብዙ ነገሮች እንዲቆጩኝ ያደርጋል፡፡ ለምሳሌ ስለዛሬው የአብዛኞቻችን ሕይወት አስቸጋሪነትና በሁሉም ነገር ተወዳድሮ በላጭ መሆን እንደሚያስፈልግ በጥቂት ስንኝ እንዲህ እያለ ይተነብይልኝ ነበር እኔም አንዲት ሀረግ ሳልስት አስታውሳት ነበር፡፡ ‹‹በእንዲህ ያለ ዘመን አይተኙም ይነቋል፤ በላተኛው ሁሉ በያፋፉ ዘልቋል›› ትላለች፡፡ ታድያ ይህች ግጥም ይህን ዘመን እንዴት ቁልጭ አርጋ እንደምታሳየን እናንተው ታዘቡ፡፡ሆኖም ግን ከብዙ ታላላቅ ትዝታዎቼ አንዱን ከአእምሮዬ ማህደር መዘዝ አድርጌ አዝናኝ የሆነውን የሕይወት ትምህርቴን ላጫውታችሁ፡፡ ወንድ አያቴና ሴት አያቴ ከትውልድ ስፍራቸው ተሰደው ኑሯቸውን ከሚመሩበት ትንሽ ወረዳ ወደ ኋላ በጊዜ ዥረት ልውሰዳችሁ፡፡ ተሰደውም መቂ ወረዳ በ ወዮ ገብርኤል መንደር ውስጥ መኖር የጀመሩት አያቶቼ ጋር የትምህርት ማለቅን ተከትሎ እረፍቴን ከእነርሱ ጋር ለማሳለፍ

ጀርመን፣ሂትለር፣እግርኳስ፣ኤንጌላ ሜርኬል

የዛሬዎቹን ጀርመናውያንን ሳስብ ከ 2 ኛው የአለም ጦርነት በኋላ ድምጻቸውን አጥፍተው ዓለም ከደረሰበት ደረጃ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉብ ያሉት ጀርመናውያን ትዝ ይሉኛል፡፡ ሀገራቸውን ‹‹ላንድ ኦፍ አይዲያ›› ሲሉ ይጠሯታል፡፡ ለነገሩ ምን ያህሎቻችሁ እንደምታውቁ እርግጠኛ ባልሆንም አብዛኞቹ የሳይንሳዊ ስልጣኔ ሃሳብ መነሻ ጀርመን ናት፡፡ ዶሽላንድ ከተበታተነችበት ውድቀት አንድ እስካደረጋት አጭሩ፣‹‹ጨካኝ›› መሪ ኦቶ ቮን ቢስማርክ እስከ እኩዩ ሂትለር ድረስም ሆነ ከዛ በኋላ ጀርመን ለአለም ስልጣኔ ትልቅ አስተዋዕፆ ነበራት፡፡ የትላንቱን የጀርመንና የፖርቱጋል እግር ኳስ ፍልሚያ ስንመለከት፡፡ የሁለት ታላላቅ ሃያላን ሀገራት ልዮነትን በግልፅ አይተናል፤ፖርቱጋል የኋለኛው ዘመን፣ጀርመን የዚህኛው፡፡ ‹‹ ቆራጧ››፣ ‹‹ደፋር››፣ ‹‹ብልህ››፣ ‹‹ውሳኔ የማትፈራ›› አልፎ አልፎም ‹‹አምባገነን›› የሚሏት ኤንጌላ ሜርኬል በፎንቴ ኖቫ ሳልቫዶር ስታድየም ለጠጥ ብላ ቁጭ እንዳለች በንቃት የጀመርናውያኑን የኳስ ትርዒት እየተከታተለች ነው፡፡እንደብዙዎቹ እነስቶች ( በተለይ እንደ የአፍሪካ ቀዳማዊ እመቤቶች ) ደማቅና ውድ የሆኑ ልብሶች የማትወድ እንስት ናት፡፡ እግር ኳስ ብሔራዊ ፍቅር በሆኑባቸው የአለም ሀገራት እንዲህ የሚያደርጉ መሪዎች ያሏቸው ከአፍሪካ በስተቀር ብዙ የአለም መሪዎች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ ሆኖም በጀርመናውያን ዘንድ ያልተለመደ ቢመስልም ኤንጌላ ሜርኬል ግን ከሂትለር በኋላ እስካሁን ከነበሩት የጀርመን መራሂ መንግስት ለየት ያለ ባህሪ ያላት ናት፡፡ ይህች ሴት ስልጣን ላይ ከመጣች በኋላ ጀርመን በምጣኔ ሃብትና በብዙ ዕድገቶች ተምዘግዝጋለች፡፡ ብዙ ጀርመናውያን እንስቶች በተለያዩ የመንግስት ቦታዎች ወደ ስልጣን መጥተዋል፤እንደውም

‹‹የዓለም ዋንጫና የኤፍ.ኤም ጋዜጠኞቻችን ፋውል››

ጥሎብኝ አሁን አሁን እንደ አሸን የፈሉትን የኤፍ.ኤም ጋዜጠኞች ማዳመጥ አልወድም፡፡ አስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ስገባ ካሆነ በስተቀር፤ለምሳሌ ታክሲ ውስጥ፤ካፌ አልያም ሬድዮንን መዝጋት የማልችልበት ቦታዎች ስሆን ማለቴ ነው፡፡ እናም ከአካውንቲንግ፣ማርኬቲንግ፣ቢዝነስ፣ፊዚክስ፣ ባዮሎጂ ወዘተርፈ የመጡ ስራ አጦች የሚሰባሰቡበት ሞያ እየሆነ ስለመጣም የሬድዮ ጋዜጠኝነት ለአድማጮች የጆሮ ህመም ከሆነ ሰንብቷል፡፡ እናላችሁ ትላንት በታክሲ እየሄድኩ፣ከሚንኮረኮረው የታክሲው ልሳን የዛሚ 96.3 ሬድዮን ሳዳምጥ የሰማሁትን አሳፋሪና አስቂኝ የጋዜጠኞች የቀጥታ ወግ ላካፍላችሁ፡፡ አንድ ወንድና አንዲት እንስት ሆነው ወቅታዊ ወሬዎችን በቀጥታ ስርጭት እየጠረቁ ነው፡፡ ወንዱ ጋዜጠኛም እንዲህ ሲል ጀመረ፡፡ ‹‹እንግዲህ እንትናዬ(የጋዜጠኛዋን ስም በቁልምጫ ጠርቶ) የዓለም ዋንጫ በብራዚል ይካሔዳል›› በማለት ሲጀምር ደነገጥኩ፡፡ እንዴ ዛሬ ስንት ቀኑ ነው የዓለም ዋንጫ መካሄድ ከተጀመረ? ስል ራሴን ጠየቅኩ፡፡  ጋዜጠኛ በመሰረቱ እንዲህ ያሉ ቀላል መሠረታዊ ስህተቶችን ሲፈፅም ልቡ ስቱድዮ ውስጥ የለም ማለት ነው፡፡ አልያም በደመ ነፍስ በወረቀት ላይ የጫረውን ሳያርም እያነበበ መሆን አለበት፡፡ ‹‹ ወደ 60 ሺህ በላይ ተመልካች የሚይዘው የሳኦ ፓውሎ ስታድየም ብዙ ሺህ ተመልካችን አስተናግዷል›› ሲል በመቀጠል ላይ ከተናገረው እውነታ ጋር የሚፋለስ ሌላ ጋዜጠኛዊ ፋውል ሰራ፡፡ እኔ ብሆን እስካሁን ይህን ጋዜጠኛ በአንድ ቢጫ እና በሌላ ማስጠንቀቂያ አስደነብረው ነበር፡፡ ለመሆኑ አዘጋጅ የሌለው ፕሮግራም ይሆን ስል ሳቅ አልኩ፡፡ ‹‹አሃ!›› ሴቷ ጋዜጠኛ ተቀብላ ማውራት ጀመረች፡፡ ‹‹ ስንት ሚልዮን ማለት ነው የሚይዘው?›› ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ ሳቄን ለቀቅኩት

ልጅነታቸውን የተቀሙ ልጆች

ሁሌም ወደ ቢሮዬ ሳመራ ብሔራዊ አካባቢ የማየው አንድ ትዕይንት አለ፡፡ አሁን አሁን የተለመደ ነው፡፡ በተለይ በታክሲ ውስጥ ሳልፍ፤‹ምነው እነዚህን መንግስት ዝም አላቸው› የሚለው ተሳፋሪ ብዙ ነው፤ አንዳንዱ ደግሞ ‹እነዚህንማ አንድ ቦታ ወስዶ ማጎር ነው!›ይላል እናንተም ሳታዩዋቸው አትቀሩም… ቁጥራቸው ከዕለት ዕለት እየጨመረ መጥቷል፡፡ እነዚህ ታዳጊዎች ራሳቸውን እንደሚጠሩት ‹ቦርኮዎች› እዚህ ብሔራዊ አካባቢ ባሉ የትራፊክ መብራቶች ሥር ቁጭ ብለው መብራት የያዘውን መኪና ጠጋ በማለት የፊት መስኮቶቹን በመወልወል ሳንቲም ይለምናሉ፤ ታዲያ ይህ ምኑ ይገርማል እንዳትሉኝ፤ ጉዳዩ ወዲህ ነው፡፡ እነዚህ ሕፃናት ከትንሽ ትልቁ ሁሉም እጅ ላይ አንድ ነገር አይጠፋም፤በተጎረደ ሃይላንድ የተሞላ ማስቲሽ፡፡ ባለፈው እንደተለመደው ወደ ቢሮ ሳመራ መብራት ያዘን፤ድንገት ከየት መጡ ሳንለው ወረሩን፤ሊያባርረቸው የሚወራጨውን ሹፊራችንን ‹‹ተዋቸው›› አልኩና የመኪናውን መስታወት ወልውሎ እጁን ለሳንቲም የዘረጋውን ታዳጊ መስታወቱን ዝቅ አድርጌ ጠራሁት፤ ሰፍ ብሎ ሲመጣ አንድ ብር ስሰጠው፤ ‹‹ይመችሽ ያራዳ ልጅ የገባሽ ነሽ እኮ›› ምርቃት እንደሆነ የገባኝ ከዚህ ሌላ ምንም የሚለኝ እንደሌለ ስገነዘብ ነው ‹‹እሱ የያዝከው ነገር ምንድን ነው?›› ‹‹አታርፊውም እንዴ ጀለስ፣ማስቲሽ ነው እኮ›› አለኝ ‹‹ምን ያረግላችኋል?›› ‹‹ኸረ ሙድ እየያዝሽ መሆን አለበት ፤ያራዳ ልጅ አይደለሽ እንዴት አታርፊም፤ምግብ እኮ ነው!›› ያራዳ ልጅ ልሁን አልሁን አሁን ይህን ከዚህ ጋር ምን ያገናኘዋል አልኩና ለራሴ፤ማስቲሽ ያለው ኬሚካላዊ ይዘት ርሃብን ከማስቀረት አንፃር እሚያስረዳኝ ሰው ባለመኖሩ ግራ እንደተጋባሁ ሳስብ፤ ‹‹ማስቲሽ ካልሳብንማ አለቀልን ማለት

አቦን ያየ በልጥ በረየ

ጊዜው ከሰማንያዎቹ መጨረሻ አለፍ ብሎ ከዘጠናዎቹ መጀመርያ ውስጥ ነው፡፡ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ካሏት ት/ቤቶች ሁሉ ለየት ያለ ነው፤አቦ ት/ቤት፡፡ እኛ አቦ ት/ቤት ስንለው መስራቹ ደርግ ደግሞ መካነ ሕይወት አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ብሎ ሰይሞት እንደነበረ በሩ ላይ የተደነገረው ጹኹፍ ይመሰክራል፡፡ አቦ ት/ቤት ከአቡዬ ቤተ ክርስቲያን ጎን በመሠራቱና ቀደም ሲል ቦታው የቤተክርስቲያኑ መቃብር የነበረ ሲሆን ደርግ መቃብሩን በማረስ ት/ቤቱን እንደገነባበት ይነገራል፡፡ ታድያ በዚህ ት/ቤት እንደማንኛውም የፈረንሳይ ልጅ የ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ትምህርቴን ተከታትያለሁ፡፡ አቦ (ት/ቤቱን ነው) በባህሪው ወልዶ መጣያ እንደሚባሉት ዓይነት ነበር፤የዛሬን አያርገውና! የትኛውም ወላጅ ልጁን እየሱስ 41 ወደሚገኘው ሚሽን ት/ቤት ለማስተማር ይሞክራል፡፡ በዘመድ አፈላልጎም ቢሆን፤ካልሆነ ወደ አቦ ጦር ሜዳ ስንቁን አስይዞ መላክ ነው፡፡አጥር የሌለው፣ መስኮቶቹ የተሰባበሩ፣ነውጠኛ ተማሪዎች የሚማሩበት፤በተለይ የአቦ ሰፈር ዱርዬዎችን ያፈራ እንደሆነ የት/ቤቱ ታሪክ ይጠቁመናል፡፡ ታድያ ይህን ካልኳችሁ በአንድ ወቅት የገጠመኝን፣አስቂኝ፣አስደንጋጭና በት/ቤቱ ወሳኝ ለውጥን ያመጣ ክስተት ላውጋችሁ፡፡ 7ኛ ክፍል እያለን እጅጉን ደስታ ከሚሰጡን ነገሮች መካከል ኳስ መጫወትና ኳስ መጫወት ነው፡፡ ታድያ የኛ 7ኤ ክፍል ደግሞ እጅጉን የለየለት ረባሽ፣ ደስታና ጨዋታን የሚመርጡ ታዳጊዎች የተሰባሰብንበት ክፍል ነበር፡፡ ጥሎብኝ ሁልጊዜም ረባሽ ክፍል ይደርሰኛል፡፡ ማን ያውቃል ረብሻው ጥሎበት ሁሌ እኔ አጋጥመው ይሆናል፡፡ ባገኘነው አጋጣሚም በት/ቤቱ የታችኛው ክፍል ወርደን እንጫወታለን፤እንራገጣለን፤ላባችን ጠብ እስኪል እንፈነጥዛለን፤ነገ መኖር እሚሉት ሀሳብ እንደሌለ እስክን

ወይ ሃይስኩል

መቼም የሃይስኩል ትዝታዎች የሌለው ሀበሻ ማግኘት ባይከብድም፤ አብዛኞቻችን አልፈንበታል፡፡ ሃይስኩል ትዝ ሲለኝ ብዙ ነገሮች ከአንጎሌ የትዝታ ሳጥን ብቅ ይሉብኛል፡፡እኛ ካራማራ እንለዋለን አስተዳዳሪዎቹ ደግሞ ከፍተኛ 12 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ይሉታል፡፡ መቼም ፈረንሳይ ለጋሲዮንን ያየ ካራማራን ሳያይ አያልፍም፡፡ አሁንም ድረስ ማለት ይቻላል እነዛ የጡብ ሕንፃዎችን ሳይ ትዝ ትዝ የሚሉኝ ነገሮች ስፍር ቁጥር የላቸውም፡፡ ካሯሯጡ የማይለቁ ሯጭ ዘበኞቻችንን ማን ይረሳል? እንደው እነ ደፈርሶ ያኑ ነቄ ቢሆኑ ኑሮ ተማሪ ከማሳደድ ጀምረው ዛሬ እንዴት የተዋጣላቸው አትሌት በሆኑ ነበር፡፡ ዱላ ካነሱ ሳይረበርቡን የማይመለሱ መምህራኖቻችንን ማን ይረሳል? ያቼን ሚኒሜዲያስ ብትሆን?...እንደውም ዛሬ ስለዛች ሚኒሚዲያ ሸረፍ አድርጌ አንድ ገጠመኝ እንካችሁ ልበል፡፡ ለነገሩ ለዛሬ ጋዜጠኝነት ለሚሉት ልክፍት የሆነ ሞያ የዳረችኝ ያቺ ሚኒ ሚዲያ ናት ብል አይጋነንም፡፡ ግን ብዙ ነገሮችን ተምሬባታለሁም ማለት እችላለሁ፡፡ ..እንደው አንዴ ምን ሆነ መሰላችሁ፤ እንደሚታወቀው የእረፍተ ሰዓት ላይ ሚኒሚዲያችን ትንግሳለች፡፡በወቅቱ የተጨበጨበላቸው የሚባሉ(የሚያጨበጭቡላቸው ጀሌ ተማሪዎች ስላሉ ነው) የት/ቤቱ ጋዜጠኞች ቀጥታ በሚተላለፍ ሙዚቃ ጀርባ ከባድ ጭቅጭቅ ውስጥ ገብተዋል፡፡ እኔ ሆዬ አርፍጄ ወደ ስቱዲያችን(ይቅርታ ከ ስቱዲዩ ሌላ ቃል ስላጣሁ ነው) እየገባሁ ሳለ ወሬው ሳበኝና ሳቄን እንደያዝኩ ቆምኩ፤ ጭቅጭቁ ስለአንዲት የ9ኛ ክፍል ቆንጂት ነው፡፡ መቼስ የሴትና የወንድ ወሬ አይደለም በዛ እድሜ በዚህም ቢሆን ልብ ነው የሚያቆመው፡፡ እየተካረሩ እየተካረሩ ይመጣሉ፤ አስቂኙ ነገር ደግሞ ስለ ልጅቷ እና ስለአንደኛው የሚኒሜዲያው ጋዜጠኛ አደባባይ የማይወጣ

...............የፈረንሳይ ልጆች…...........

ከኮንጎ ሰፈር እድርተኞችና ከ ኑ ቡና ጠጡ ቡድኖች ያጋራኋት ጡሁፌን እናንተም እንዲህ ተጋሯት መቼም ባልወለድበትም ግማሹን ዕድሜዬን ስለኖኩርበት የፈ ረንሳይ ልጅ ነኝ ልበል፡፡ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ብዙ መለያዎች ቢኖሯትም ከብዙዎቹ የሸገር የድሆች መጠለያ ወፈ ሰማይ የሚሆነውን የድሃ ቁጥር ይዛለች ብዬ እገምታለሁ፡፡ ሆኖም ከዚህ ባለፈ ደግሞ እንደ ሽሮሜዳ ያለ ሰፈሮች አጎራባች ከመሆኗም ባሻገር ብዙ የሚያስተሳስሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስሮች እንዳሉ የሁለቱ ሰፈሮች የፖለቲካና ማህበራዊ ተንታኞች በብዙ ጠጅ ቤቶች ውስጥ ጥናታዊ ወሪያቸውን ሲለግሱን ኖረዋል፡፡ ለመሆኑ የፈረንሳይ ልጅ ለመባል ብዙ መለኪዎች እንዳለ ያውቁ ኖሯል?እስኪ እኔ ከማውቀውና ከትንሹ በጥቂቱ እንዲህ ላውጋችሁ፤ቢያንስ ከነዚህ ውስጥ አንዱን አልያም ሁለቱን ሲሆን ደግሞ ሁሉንም ያልፈፀም ፈረንሳይ አድጌያለሁ ቢል ዘበት ነው፤ እናላችሁ የፈረንሳይ ልጅ ሆኖ አዘነጋሽ ሜዳ ላይ ቅሪላ ያልገፋ፣ ጨፌ ሜዳ ላይ ዋንጫ ያላነሳ፣ ጉራራ ሜዳ ላይ የኳስ ብቃቱን ያልፈተሸ፣ጊዮርጊስ ሜዳ ላይ ያልፈነጨ ፣እስላም መቃብር ላይ ያልተራገጠ፣ቦኖሃ ወርዶ ኳስ ያልጫወተ፣ ከሽሮ ሜዳ ልጆች ጋር ኳስ ያልገጠመ፣ እንዴት የፈረንሳይ ልጅ ነኝ ይላል? ሌላው ቢቀር ጥንስስ ወርዶ ዋናን ያልለመደ፣ ስድስት ክንድን በ ሰቶ ያላቋረጠ፣ አባ ንጉሱ ላይ ያልተንቦራጨቀ፣ ኩባ ባህር ላይ የኋሊት ያልተንሳፈፈ የፈረንሳይ ልጅ ነኝ ሊል እንዴት ብሎ? አልያም ደግሞ ቀበናን አሳብሮ አጋምና ቀጋ ለቅሞ ያልበላ፣ ዋሻ ሚካኬል ደርሶ በመገናኛ ሜዳ ላይ ያልሮጠ፣ከሾላ ዛፍ ላይ ሾላ አውርዶ ያልበላ፣በልቶም መጥገቡን ለማሳየት ከቅርንጫፍ ቅርንጫፍ ያልዘለለ የፈረንሳይ ልጅነትን ጣዕም እንዳላጣጣመ ይወቀው ይረዳው፡፡ በሰፈ

የሳውና ባዝ ትዝብቶች

የፍልውሃ ደንበኛ ነኝ፡፡ ቋሚ ተሰላፊ ነኝ ማለትም እችላለሁ፡፡ ምንስ ቢሆን የነጣይቱን ያህል በተፈጥሮ ፍል ውሃ ባንገለገልም በኤሌክትሪክ ፍሊትም እንቀቀል እንጂ፡፡ አሁን አሁን ግን ቤቱ እርጅና ተጭኖት ብዙው መገልገያቹ አርጅተው፤ ፍልውሃ ከተገለገሉ በኋላ ቤትዎ ሄደው ሸውራራ ሻወር እንዲወስዱ የሚገደዱበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ያም ሆነ ይህ ከሳውና ባዝ በየጊዜው የቃረምኳቸው ትዝብቶች ብዙ ናቸው፡፡ በመሰረቱ ሳውና ባዝ ሆነም ሌሎች የእጥበት ሥርዓቶች ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ገና በ11ኛው ክፍለ ዘመን በጎንደራውያን የስልጣኔ እርከን መሆኑን ምን ያህሎቻችሁ እንደምታውቁ ባላውቅም የጎንደርን ቤተመንግስት የጎበኘ ግ ን ይህንን ነገር ማወቅ ይችላል፡፡ እነ ፋርስ፣ህንድ፣ቻይና እና የአረብ ምድር እኩል ከኛ ጋር ይህን የስልጣኔ ትሩፋት ኮምኩሟል፡፡ ታሪክ ማውሳቱን እንተወውና ወደ አዲስ አበቤዎች የሳውና ባዝ ተጠቃሚዎች ልምጣ፡፡ በዛች ጠባብ ክፍል ውስጥ በወንዶች ክፍል የሚታየውን ትዕይንት እኔ ላካፍላችሁ፤በሴቶቹ በኩል ያለውን እንስት ፀሐፍት ተገኝታ እስክታካፍላችሁ ጠብቁ፡፡ እናላችሁ ገና ከመታጠቢያ ገንዳው ሳይደርሱ የሚታዘቡት አዝናኝ ምስል ፈገግታን በነጻ ይስኮመኩምዎታል፤ጥርብ እግር፣ፍልጥ እግር፣ግንድ እግር አልያም ደግሞ የወንድ ነፍሰ ጡር የሚመስል በደምሳሰው ደግሞ ፤3 ቁጥር 9 ቁጥር፣ 10 ቁጥር እንደው ምን አለፋችሁ የተለያዩ የአረብኛውን ቁጥር የሚወክሉ ቅርፅ ያላቸው ወጣቶች፣አዛውንትና ጎልማሶችን እያያችሁ፤ሀበሻና ስፖርት ጠብ ውስጥ እንደሆኑ ስትረዱ ፈገግ ይላሉ፡፡ ወደ መታጠቢያው ገንዳ ሲያመሩ ደግሞ የሚያዩት ትዕይንት ፈገግታ ብቻ ላይፈጥርብዎ ይችላልና እንደመሳቅ ሊቃጣዎም ይችላል፡፡ የሰዎቻችን የአስተጣጠብ ክህሎት ሀበሾች የውሃ ዕጥረት