‹‹የኛ ሰው በፌስቡክ››
እንደው እናንተዬ እኔን ብቻ ይሆን የሸተተኝ እናንተንም ጭምር? ‹‹ ስም ከስብ ይሸታል›› ይላሉ አበው፡፡ መለስ አርገው ደግሞ ‹‹መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ›› ይላሉ አይ አበው ለሁሉም ማስረጃ አያጡ!....ስምና ማንነት እጅግ የተነጣጠሉ ነገሮች ቢሆኑም አንዳንዴ ግን ምግባርን ተከትሎ የሚወጡ ስያሜዎች ግን አግባብነት አላቸው፡፡ የማሕበራ ድረ ገፆችን መስፋፋት ተከትሎ እኛም እንደሌሎቹ ህዝቦች መረባችንን ዘርግተን ተጠቃሚ ብንሆንም፡፡ ሁልጊዜም ሀባሻ ያየው ነገር እንዲሉ ስምና ስያሜያችንን ከኩፍስ ማንነታችን ጋር ይዘነው ዘልቀናል፡፡ እናም የኛ ሰው በፌስቡክ የሚቀመው ስምና ማንቆለጳጰሲያ መንገድ እጅግ ግር ም ይለኛል፡፡ የእንስቶቻችን ስያሜ እንደምሳሌ ላንሳውና ‹እከሊት ቆንጆ› ‹እገሊት ስዊት› ‹እንቶኒት ላቭ› ‹እንቶኒት ማር፣ ዲር.... ምናምን የሚሉ ስያሜዎች ራስን ከማንቆለጳጰስ ያለፉም ይመስላሉ አሉላቹ ደግሞ ወንዶቻችን ‹እከሌ ዘማን!› ‹እንቶኔ ዘቤስት!› አልያም ደግሞ ‹እከሌ የተሰኘውን ራፐር ወይም ምዕራባዊ ዘፋኝ ከስሙ ጋር በመቀየጥ የጨበራ ተስካር የመሰለ ስም ይዞ ይመጣልዎታል ድንገት የፌስቡክ ገፅዎን ከፍተው ይሔን ስም ለማንበብ ሲታገሉ ራስዎን ሊያመዎትም ይችላል፡፡ የበለጠ የሚያስገርመው ነገር ደግሞ ይህን መሰል የተንቆለጳጰሰ ስያሜ ያላቸው ምዕራዉያንም ሆኑ አፍሪካውያን የፌስቡክ እድምተኞች አለማየቴ ነው፡፡ እናም ሀበሾች የተለየ የሚያረገንን የቤት አመል ይዘን እዚሁ ወጣን!?በስነልቦናው ሳይንስ አንድን ማንነት መሆን አለመቻላችን እንድናስመስል የሚያስገድደን የስነልቦና ጉድለት እንዳለ ይጠቅሳል፣ የኛም ችግር ከዚህ የተለየ አይመስለኝም፡፡ እንደውም እዚሁ ፍስቡክ ላይ ያገኘኋት ደስ የምትል አባ