Posts

Showing posts from February, 2016

ጥያቄ አለኝ

በእውነቱ ወንደኝነት ያጠቃናል፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝና ‹‹ወንደኝነት››የሚል የአማርኛ የቃል አረባብ ባይኖርም፤ያራባሁት እኔው ነኝ፡፡በቤተ ሙከራዬ፡፡ አብዛኞቹ የአማርኛ ቃላት አላግባብ ፀሐይ ላይ በመዋላቸው የተነሳ ያልባከነ ቃል ስላጠረኝ እንደሆነ ብቻ ተረዱልኝ፡፡ በእውነቱ እኛ ወንዶችም ሆንን አንዳንድ ሴቶች ወንደኝነት(ፆተኝነት) ያጠቃናል፡፡ ለምን ብትሉኝ፤እህ ብትሉኝ አንድ ጥያቄ አለኝ፡፡ ስንቶቻችን ነን የሴት አያቶቻችንን ስም የምናውቅ?ባባት በሚጠራ ማህበረሰብ ውስጥ እስኪ የአያቶችህን ስም ጥራ/ጥሪ ብንባል… ‹‹ጉልማ፣ዳንዴው-ዳንዴው፣ሃይሌ-ሃይሌ-ሴሬቦ…›› በቃ ወንድ አያቶቻችን ብቻ፤ ሴት አያቶቻችንንስ? የእናትህ እናትስ? የአባትህ እናትስ? በሴት አያቶቼ ስም እምላለሁ ከአንድ በላይ የእናቱንና የአባቱን እናት፣እናት፣የእናት እናት፣የእናት እናት እ ናት የሚያውቅ ካለ እኔ እቀጣለሁ፡፡ ታላላቅ ስብዕናን የተጎናፀፉ ሴት አያቶቻችን እንደዋዛ ስማቸው ይጠፋል፡፡ በእውነቱ ወንደኝነት ያጠቃናል፡፡ በዚህ ብቻ አያበቃም፡፡ በወንድ የበላይነት የምትጦዘው ዓለም የሰው ልጅ ወንደኝነት የሚያጠቃው ብቸኛ እንሰሳ ይመስላል፡፡ለምን ብትሉ ይኄ በአንዳንድ እንሰሳት አይሠራማ!፡፡ ለምሳሌ በማህበረጅብ ዋነኛ መሬ ሴት ጅብ ናት፡፡ ወንድ ጅብ የበይ ተመልካች ነው፡፡ ጅብ እንኳን በእንስቶች ይመራል! ይህንንስ ምን ያህሎቻችን እናውቃለን? አስገራሚው ጉዳይ ደግሞ ከዛሬ 10ሺህ ዓመታት በፊት እነ ግሪክ ሳይሰለጥኑ የነበረው የሰው ልጅ ታሪክ ነው፡፡የዛሬን አያርገውና አለም ያኔ በሴቶች ትመራ ነበር፡፡ ቢቢሲ እንኳን ተደንቆ ይህን ታሪክ <<When God was a woman>> ሲል ተርኮታል፡፡ የዛሬን አያርገውና አለም ያኔ በሴቶች ስት

ርዕስ አልባ ግጥም

ግጥም ከሃይለኛ ብዕረኛ የሚፈስ አንዳች ነገር ይመስለኛል፡፡ ፀሐፍት ሁሉ ገጣሚ መሆን አይችሉም፡፡ እርግጥ ገጣሚያንም ሁሉ ፀሐፍትን መሆን አይችሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን በሽነጣ ጣል የሚደረጉ ግጥሞች ነፍስ አላቸው፡፡ ለዛሬም ሲሸንጠኝ ጣል ያረግኋትን፤ዝናብ አልባ ሰማያትን ለመለማመን አንድ ያልኳት ግጥም ርዕስ አልባ ብትሆንም እንካችሁ ብያለሁ፡፡ ......... አያለቅስም አሉኝ ያገሬ ሰማይ፣ ያለዕንባ ዘለላ ይለቀሳል ወይ፣ ለካ እምባም ይገዳል ስማይም ሲከፋ፣ ወዲያ አላለቀሰ፤ወይ ዘለላው አልጠፋ፡፡ ቀረ ሲሉት አለ፣ መጣ ሲሉት ቀረ፣ ዕንባ እንዳቀረረ (ማልቀስ ላቃተው የሰሜን ምስራቁን ሰማይ ለማባበል የተገጠመ)