Posts

Showing posts from July, 2014

ቡና..ቡና

ልጅነትን ከሚያጣፍጡት እውነታዎች አንዱ ለነገሮች የምንሰጠው ልጅነታዊ እይታ ነው፡፡ መብላት፣ መጠጣት ፣መጫወት እንደምንም ብሎ ትምህርት ቤት አለመሄድ፤ በተለይ ነገ ትምህርት የለንም ወንዳታ! አቤት ደስ ሲል ፡፡ ልጅነት ደስ የሚል ጅልነትም ነው፡፡ ስለ ሒይወት የምንሰጠው ትርጉም፣ስለስነፍጥረት በራሳችን እውነት ነው ብለን የምንይዘው አቋም ወዘተ ልጅነትን እንድናፍቅ ያደርገኛል፡፡ ከልጅነት አሳዛኙና ቁጭትን የሚጭረው ነገር ቢኖር ልጆች እንደ ልጅ ተጫውተው፣ተጣልተው፣ተፋቅረው፣ሁሉን ነገር ሆነው ማደግ ያልቻሉ የያኔ አበባዎች የዛሬ ጎልማሶችና ወጣቶች ወይም አዛውንቶች ሕይወት ብቻ ነው፡፡ ያም ሆነ ይህ ስለ እነዚህ አይነት ልጆች ወደፊት የሚለው ነገር ብዙ ቢኖረኝም ለዛሬ ግን አንድ ጥሩ ትውስታ ልጫርባችሁ፡፡ ይህ ትውስታ የኔ ብቻ ሳይሆን የብዙዎቻችሁ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ድሮ ድሮ ነው፡፡ ጧት ጧት፡፡ በተለይ ሰኞ ሰኞ ፡፡ ወደ ትምህርት ቤት መሔድ ከሚጠሉት ተማሪዎች መካከል አንዱ ነበርኩ፡፡ በተለይ ሀይስኩል ላይ ትልቁ ፈተናዬ ከአልጋዬ ላይ መውረድ ነው፡፡ እኔ ከአልጋዬ ላይ ከምወርድ ሀገር በአፍጢሟ ብትደፋ ይቀላል፡፡ ሁል ጊዜ ጧት ጧት ውዷ እናቴ ጋር ከባድ ጦርነት እንገጥማለን፡፡ ፋዘር በዚህ ሰጣ ገባ ውስጥ ጣልቃ ለለመግባት ይጥራል፡፡ እርሷ ዝም ባትለውም ገለልተኛ አካል ለመሆን ይጥራል፡፡ ጧት በተለይ ሰኞ ጧት ይህ የተለመደ የማዘርና የኔ ጦርነት ዛሬ ላይ ፈገግ ከሚያደርጉኝ ትዝታዎቼ ውስጥ ትልቁ ነው፡፡ የሁለት ሰዓት ዜና ተነቦ ሲጠናቀቅ ይህ የተለመደና አንዳች ሃይል ያለውን ዜማ ስሰማ ስቅቅ ይለኛል፤ ብቻ በእንቅልፍ ልቤ ሆኜ አዳምጠዋለሁ፡፡ ‹‹የኢኮኖሚ ዋንጫ ቡና ቡና. ……………………. አውዳ ነው ቡናችን ቡና ቡና›› ግጥሙን በደን

................‹‹አክተርና ድሃ››.................

እጅግ ረጅም ሰዓት ስለቆምኩና አማራጭ ስላጣሁ የመጣው ይምጣ ብዬ ተሳፈርኩባት፡፡ ጀልባ ላይ እንጂ ታክሲ ውስጥ መሆኔን የተጠራጠርኩት፤የሰማይ ስባሪ የሚወዳደራት አንዲት ሴት ወይዘሮ ገና ስትረግጣትና የታክሲዋ የጭንቀት ውዝዋዜ አንድ ሲሆን ነው፡፡ ባስ ብላ ደግሞ እኔው አጠገብ ስትቀመጥ የተሸከምኳት እንጂ ያስጠጋኋት አልመስልህ አለኝ... ይቅርታ ይደረግልኝና በመሠረቱ ይህን መሰል ሰው አጠገቤ ሲቀመጥ ምቾት አይሰጠኝም...ጸጉሩን 99 ዙር የጠቀለለ፣ያጥመዘመዘና ያልመዘመዘ ወጣት እንደባንዲራ ዝቅ ያለውን ‹ጅል ሱሪውን› እንደነገሩ ከፍ ለማድረግ እየሞከረ ጋቢናውን ሲይዝ ሹፌር መሆኑን አረጋገጥኩ...ይህ ግለሰብ ከዚህ በላይ ፀጉሩን ቢጠቀልል ወደፊት ተከርብቶ አደጋ ውስጥ ሊከተን እንደሚችል ገምቼ ብቻዬን ፈራሁ... ታንኳ መሰል ታክሲ ውስጥ ያለሁ እስኪመስለኝ ድንገት እየተርገፈገፈች በመነሳት ጉዟችንን በግድ አስጀመረችው፡፡ ቀና ብዬ አሮጌ ቤተመቅደስ የሚመስለው ጋቢናዋን ስመለከት በጥቅሶች ተንቆጥቁጧል፡፡ አስገራሚው ነገር ታክሲዎቻችን ተሳፋሪዎቻቸውን በነገር ጎሸም ለማድረግ፣ለማስጠንቀቅ፣ፈገግ ለማሰኘት አንዳንዱ ደግሞ ለማስደነቅ አይንና አእምሮ የሚሸነቁጡ ጥቅሶችን ከላይ እስከታች ይደረድራሉ... ብዙ ጊዜ ግን ከማሳቅ ይልቅ ባለማሳቅ የሚያስቁ፣የሚያሳቅቁ እውነቶችን ሸክፈው የያዙ አባባሎችም ይበዛሉ... እናም ከጥቅሶቹ ውስጥ ደህና ነገር ካለ ብዬ ሳማትር አንዲት የተጎሳቆለች ጥቅስ ከነከነችኝ… ‹‹ደሃና አክተር ይንገላታል እንጂ አይሞትም!›› በሱቅ ሚዛን ይሁን በሕይወት ሚዛን ደሃና አክተር እኩል ሲመዘኑ አይቼ ስለማላውቅ የዚች ጎስቋላ ታክሲ ድፍረት አናደደኝ... እርሷ በእርግጥ ከየትኛው ወገን እንደሆነች አልተጠራጠርኩም ግን አጉል መንጠራራት አደረገችው.

ውሸት…ሲሸት

‹‹ወይ ውሸት››፣አቤት ውሸት ፣‹‹ሂድ ውሸታም›› ፣‹‹ወግጅ ቀጣፊ›› ውሸት… በቀድሞ የኣማርኛችን አገላለፅ ደግሞ ኩሸት… አልፎ አልፎ ቅጥፈት፣ ማታለል ሌላም ሌላም   እንለዋልን፡፡ ለመሆኑ ምን ያህል ይዋሻሉ? ራስዎንስ ከውሸታምነት አንፃር ምን ያህል ዋሾ እንደሆኑ አስበውትስ ያውቁታል?ከውሸት ያመለጠ ስብዕና ይኖርስ ይሆን? ጥናቶች ምን ያህሉ የዓለም ሕዝብ ዋሾ እንደሆነ ሲጠቁሙ 60 በመቶው የሚሆነው የዓለም ሕዝብ በ 10 ደቂቃ ውስጥ አንድ ውሸት ሳይቀባጥሩ እንደማያልፉ ስነግርዎ ውሸቴን እንዳልሆነ ይረዱኛል ብዬ ተስፋ አረጋለሁ፡፡ ለነገሩ አጥኚዎቹስ ውሸታቸውን እንዳልሆነ ማን ማረጋገጥ ይችላል፡፡ ለመሆኑ ማን ነው የማይዋሸው? ሌላው ቢቀር ለእውነት ስንል እንዋሻለን የምንልም አለን፡፡ በእርግጥ በእውነትና በውሸት መካከል ያለው የልዩነት ድንበር በብዙው የጠበበ ይመስላል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ እውነት መራራና ድርቅ ያለ ሃቅ ነው፡፡ እውነት የሀሰትን ያህል የሚያማልል ገፅ ላይኖረውም ይችላል ስለዚህም ከእውነት ይልቅ ውሸት ብዙውን ጊዜ አማላይ ነው፡፡ ፈረንሳዊው   ንጉስ ናፖሊዮን ‹‹ የዓለም ታሪክ ተስማምተው የተቀበሉት ውሸት ማለት ነው›› ይላል፡፡ የታሪክ ሽሚያ ውስጥ እውነተኛው ነገርና መራራው ሃቅ ይካዳል ማለት ነው፡፡ ግራ አጋቢው ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ ደግሞ ‹‹ የተበሳጨሁት ስለዋሸሀኝ አይደለም፤ ከዚያ በኋላ ምንም ስለማላምንህ እንጂ›› ብሏል፡፡ ውሸት ከባድነቱ የቀጠፍነውን ቅጥፈት ሁልጊዜም ልናስታውሰው አለመቻላችን ነው፡፡ አብርሃም ሊንከንም ‹‹ማንም ሰው በማስታወስ ብቃቱ ብቻ የተዋጣለት ውሸታም መሆን አይችልም›› ብሏል፡፡ ውሸታምን እንዴትስ ይለዩታል? ውሸትማ እኮ ይሸታል የሚል አንድ ወዳጅ አለኝ፡፡ ለመሆኑ ውሸት ይሸታልን ? ይኸው

..............‹‹የፍየል ዘመን››...............

ልጆች እያለን አባቶቻችን፣ እናቶቻችን፣አያቶቻችን ስለ የዳቦ ዘመን፣የጥፋት ዘመን፣የበረዶ ዘመን፣ የድንጋይ ዘመን ያወጉን ተረቶች እውነት ቢሆኑ የሚገርመኝ ይመስለኛል፡፡ በእርግጥ ይህን ለማመን ማረጋገጫ ያስፈልጋል፡፡ ግድም ነው፡፡ እኔ ግን ስለ ፍየል ዘመን ስነግራችሁ ምንም ውሸት እንደሌለው እናንተ ራሳችሁ ምስክር እንደምትሆኑን አምናለሁ፡፡ ‹‹ለምን?›› ብትሉ የኛ ዘመን የፍየል ዘመን እንደሆነ ብዙ ማረጋገጫዎች አሉኛ! አንዱ ወዳጄ ከፍቅር ወዳጁ ጋር ሲያወጋ ፍቅር እንደያዘው ሳያቅማማ ነገራት ‹‹እኔም ፍቅር ይዞኛል ካንተ…ግን እኮ በፍየል ዘመን በግ አትሁን ይላል መፅሀፉ›› ስትል ከጣሪያ በላይ የሳቀችበት እውነት የገባው ዛሬ በአንዱ ተረኛ ስትለውጠው ነው ‹‹በእርግጥ እውነቷን ነው፡፡ በግ መሆን አልነበረብህም›› ስል እኔም በሳቅ እያውካካሁ ነገርኩት፤የገባው ግን አልመሰለኝም፤ድሮስ በግ እንዴት ይገባው!... በፍየል ዘመን ሁሉም ነገር የከፋ ነው፡፡ በፍየል ዘመን ኑሮ ውድ ነው፣ በፍየል ዘመን ፍቅርን በገንዘብ መግዛት እንደሚቻል ማየት ችለናል፤በፍየል ዘመን ተኩላዎችና ፍየሎች ጎን ለጎን እኩል እየበሉ፣እየተባሉም ይኖራሉ፡፡ ማን ነው ይሔ የጥንቱ እንግሊዛዊ ደራሲ ስሙ ጠፋብኝ… እምምምም… ጆርጅ ኦርዌል ‹‹All animals are equal but some animals are more equal than others›› ብሎም የለ… እየየውም ሲዳላ ነው አሉ የኛ ጎረቤት፡፡ በፍየል ዘመን ሁሉም ፍየሎች እኩል ቢሆኑም (በጎቹንም ጨምሮ መሆኑ ነው) አንዳንድ ፍየሎች ግን ከሌሎች ፍየሎች በተሻለ እኩል መብት አላቸው፡፡ ነው ቁም ነገሩ፡፡ በፍየል ዘመን አራት እግር ያለው ወንድ ፍየል ሁልጊዜም ተጠቃሚ ነው፡፡ ቆነጃጅት ፍየሎችን በነጻ ከበጎች ነጥቆ ይወስ

‹‹ኦቨር ወጣሁ!››

‹‹ኦቨር ወጣሁ…›› አለችው ፊቷ ላይ በሚነበብ ጀግንነት፡፡ ምን ለማለት እንደፈለገች ቢገባውም በእነዚህ   ሁለት ቀናት ውስጥ የጠፋችበትን ምክንያት ማስረዳት መጀመሯ እንደሆነ ገብቶታል፡፡ ‹‹ባይዘዌይ ለሳምንት ያህል ስልኬ ዝግ ይሆናል›› ይሄኔ ነገር ገባው መሰለች ከት ከት ብሎ ሳቀ፡፡ ፍቅር በሳምንት ውስጥ ክንፍ ያደርጋል፤ ነገር ግን ፍቅር በሁለት ቀን ውስጥ ይፈርሳል ብሎ አስቦትም አያውቅም ነበር፡፡ ፍቅር ሲያልቅ የሚታዩ ምልክቶችን እያየባት እንደሆነ ቢገባውም ከጀርባ የሆነ ነገር ሳይኖር እንደዚህ እንዳልሆነ ሆዱ ያወቀ ይመስል ‹‹የተፈጠረ ችግር አለ?›› ጠየቃት ‹‹ ኸረ በፍፁም…›› ከራሷ ጋር እየታገለች ትናገራለች፡፡ ምክንያቶቿ ሁሉ እርስ በእርስ መምታታቱ ትልቅ መልስ ነውና ዝምታን መረጠ፡፡ ከዛች የኦቨር ምሽት በኋላ   የመጣችው ፍቅሩ የእርሱ እንዳልሆነች ሲታወቀው፤ የሣምንቱ የፍቅር እብደት ማስታወስ ቀለለው ለውስጡ ሰላም ሲል፡፡ ‹‹እንደዚህ ማንንም ወድጄ አላውቅም›› ‹‹ከእንግዲህ በኋላ ጊዜዬን ላንተ ብቻ እሰጣለሁ››…….. እነዚህን የፍቅር ዜማዎች በሰማበት አንደበት   እነ ‹ኦቨር ወጣሁ›… ‹ባጋጣሚ ስላልተመቸኝ ላይህ አልችልም› የመሰሉ ማባረሪያ አዘል መልሶችን ሲሰማ ህሊናው ሞገተው ይህ አይነት የፍቅር ገጠመኞቹ ብዙ ቢሆኑም አሁን ግን ሁሉም የሰለቸው ይመስላል ‹ሳትቀደም ቅደም› ‹ራስህን አድን› ‹አሁንስ ከማን ጋር እንደሆነች አታውቅም ግን ያለምንም ጥርጥር…› ከራሱ ጋር የተጣላ ሲመስለው ወሰነ፡፡ ‹እድሜዋ ሲሮጥ ያኔ እርሷም ራሷን ለማዳን ትሮጥ የለ› አንድ እውነት አወቀ የሚያብሰለስለው የፍቅሩ ፍፃሜ ከአእምሮው እንደ ጉም ሲቦን ታክሲ ውስጥ ቁጭ እንዳለ ተገነዘበ የተሾመ በየነ አዳራ